በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው የሚኖሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተሳተፉበት ዓመታዊ የባህልና የስፖርት ፌስቲቫል በደመቀ ሁኔታ ተጠናቋል።
በፌስቲቫሉ ላይ የባህል አልባሳት፣ ባህላዊ ምግብና መጠጦች፣ የሙዚቃ ትርኢቶች እንዲሁም የህፃናትና ወጣቶች የስፖርት ውድድሮች ተካሂደዋል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አነስተኛ እና መካከለኛ የንግድ ተቋማት ምርትና አገልግሎታቸውን ያስወደሱበት የንግድ ኤክስፖ ተካሂዷል።

